አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ 366 ሺህ 737 ሰዎች ሁለተኛውን ዙር የኮቪድ-19 ክትባት መውሰዳቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡
በከተማዋ የኮቪድ-19 ክትባትን ተደራሽ ለማድረግ በተሰራው ስራ በሁለተኛው ዙር 366 ሺህ 737 ሰዎች መከተባቸውን÷ በቢሮው የእናቶች እና ህጻናት ጤና አገልግሎት ዳይሬክተር ቤተልሔም ታየ ገልጸዋል፡፡