ጤና

በመዲናዋ 366 ሺህ 737 ዜጎች ሁለተኛውን ዙር የኮቪድ-19 ክትባት መውሰዳቸው ተገለጸ

By ዮሐንስ ደርበው

October 21, 2021

 

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ 366 ሺህ 737 ሰዎች ሁለተኛውን ዙር የኮቪድ-19 ክትባት መውሰዳቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ አስታወቀ፡፡

በከተማዋ የኮቪድ-19 ክትባትን ተደራሽ ለማድረግ በተሰራው ስራ በሁለተኛው ዙር 366 ሺህ 737 ሰዎች መከተባቸውን÷ በቢሮው የእናቶች እና ህጻናት ጤና አገልግሎት ዳይሬክተር ቤተልሔም ታየ ገልጸዋል፡፡