የሀገር ውስጥ ዜና

የምስራቅ ጎጃም ዞን ተፈናቃይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ጀመረ

By Feven Bishaw

October 22, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የምስራቅ ጎጃም ዞን ትምህርት መምሪያ የህወሃት የሽብር ቡድን ጦርነት በከፈተባቸው አካባቢዎች ከትምህርት ገበታቸው የተፈናቀሉ 390 ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር መጀመሩን አስታወቀ።

የመምሪያው ሃላፊ አቶ ስለሺ ተመስገን ለኢዜአ እንደገለጹት ÷አሸባሪው ህወሃት በከፈተው ጦርነት ካደረሰው ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ውድመት በተጨማሪ የነገ አገር ተረካቢ የሆኑ ህጻናትን ከትምህርት ገበታቸው እንዲነጠሉ አድርጓል።