የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያ ለግብርናዉ ዘርፍ ልዩ ትኩረት መስጠት እንዳለባት ምሁራን አሳሰቡ

By Feven Bishaw

October 22, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምግብ እራስን ለመቻል ኢትዮጵያ ለግብርናዉ ዘርፍ ልዩ ትኩረት መስጠት እንዳለባት ምሁራን አሳስበዋል፡፡

ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ቆይታ ያደረጉት የግብርና ተመራማሪዉ ዶክተር ኤርሚያስ አባተ እንደተናገሩት÷ ግብርና ለሀገራችን የሁሉም ነገሮች አንቀሳቃሽ መሰረት ነዉ ፡፡