የሀገር ውስጥ ዜና

የናይጄሪያ የዲፕሎማቶችና ባለሀብቶች ልዑክ ጅማን እየጎበኙ ነው

By Feven Bishaw

October 24, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የናይጄሪያ አምባሳደርና የአፍሪካ ህጻናት ተሰጥኦ አግኝ ፋዉንዴሽን መስራችና ፕሬዚዳንት በዶክተር ኢንጂነር ኖዋህ ዳላጂ የተመራ የዲፕሎማቶችና ባለሀብቶች ልዑክ በጅማ ጉብኝት እያካሄዱ ነው።

የልዑክ ቡድኑ አባላት ትናንት ጅማ ሲደርሱ የጅማ ከተማ ከንቲባ አቶ ነጂባ አባ ራያ እና የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል አባ ፊጣ እንዲሁም ሌሎች የከተማው የስራ ሃላፊዎች በአባጅፋር አየር ማረፊያ ተገኝተው አቀባበል አድረገውላቸዋል።