አዲስ አበባ፣ ጥቅምት14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ዛሬ በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍል ከተማ ወረዳ 8 በክረምት በጎ ፍቃድ እድሳት የተደረገላቸውን 69 የአቅመ ደካማ ቤቶች አስረክበዋል።
ይህን ተከትሎ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው÷ በተጠናቀቀው በጀት አመት 2 ሺህ 455 የአቅመ ደካሞችን እና አረጋውያንን ቤት አፍርሰን በማደስ እና እንደገና በመገንባት አስተላልፈናል ብለዋል።