አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል በቤንች ሸኮ ዞን በጉራፈርዳ ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች ተከስቶ የነበረውን የሠላምና የፀጥታ ችግር በአካባቢው ባህል መሠረት በዘላቂነት ለመፍታት የሚያስችል የዕርቀ ሠላም ስነ-ስርዓት ተካሄደ።
ባህላዊው የዕርቀ ሠላም ስነ ስርዓት፥ በአካባቢው ማህበረሰብ ባህል መሠረት ደም የተቃቡ ወገኖች ዳግም ወደ ግጭት እንዳይመለሱ እና ወደ ቀድሞ ሰላማዊና የአብሮነት ህይወታቸው ለመመለስ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።