የሀገር ውስጥ ዜና

ባለፈው አንድ ሳምንት ብቻ ከ 4 ሺህ 700 በላይ ሰዎች በኮቪድ -19 ተይዘዋል

By Feven Bishaw

October 26, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፈው አንድ ሳምንት ብቻ ከ 4 ሺህ 700 በላይ ሰዎች በኮቪድ 19 ሲያዙ 227 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው ማለፉን የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ገለፀ።

ኢንስቲትዩቱ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንዳስታወቀው በሳምንቱ 139 ሰዎች ለፅኑ ህመም ተዳርገዋል።