የባህል እና ስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ቀጄላ መርዳሳ የብሔራዊ ስታዲየም ግንባታ ሂደትን ጎበኙ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የባህል እና ስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ቀጄላ መርዳሳ የብሔራዊ ስታዲየም ግንባታ ሂደትን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት፣ የባህል እና ስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ወርቅነሽ ብሩ፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዚደንት አቶ ኢሳያስ ጅራ እና የጽህፈት ቤት ኃላፊው አቶ ባህሩ ጥላሁን እንዲሁም ሌሎች እንግዶች መገኘታቸውን ከስፖርት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!