የሀገር ውስጥ ዜና

የአፍሪካ ቀንድ የፋይናንስ ሚኒስትሮች ውይይት ተካሄደ

By Feven Bishaw

October 28, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት የፋይናንስ ሚኒስትሮች ውይይት በበይነ መረብ ተካሄደ፡፡

በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ እንደገለፁት፥ የአፍሪካ ቀንድ ሀገራት በትራንስፖርት፣ በንግድ፣ በገጠር ፋይናንስ፣ በመጠጥ ውሀ አቅርቦት፣ የገበያ ትስስር በመፍጠርና የበረሀ አንበጣን በመከላከል ረገድ ተባብረው መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡