የሀገር ውስጥ ዜና

የጀርመን ኩባንያዎችን በኢትዮጵያ ኢንቨስት እንዲያደርጉ ያለመ የምክክር መድረክ ተከናወነ

By Feven Bishaw

October 29, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 19 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጀርመን ግዙፍ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በስፋት ኢንቨስት እንዲያደርጉ ያለመ የምክክር መድረክ በበይነመረብ ተካሂዷል።

የምክክር መድረኩን የጀርመን- አፍሪካ የቢዝነስ ማህበር ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና በጀርመን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን ከ50 በላይ የጀርመን ካምፓኒዎች ተሳትፈውበታል።