አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ከተለያዩ ያልተረጋገጡ መረጃዎችና በአንዳንድ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና ተቋማት ስም ሆን ተብሎ ከሚተላለፉ ሃሰተኛ መረጃዎች እራሱን መጠበቅ እንደሚገባው ማሳሰቢያ ተሰጠ።
በሀገሪቱ መረጋጋት እንዳይኖርና በየአካባቢው ያለው ህብረተሰብ እንዲሸበር የጥፋት ኃይሎች በመንግስት ኃላፊዎችና በተቋማት ስም የተሳሳቱ መረጃዎችን ማስተላለፍ የዕለት ከዕለት ተግባራቸው ማድረጋቸውም ተጠቁሟል።