አሸባሪው ህወሓት በኮምቦልቻ ከ100 በላይ ወጣቶች ጨፍጭፏል -የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን
አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 22 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አሸባሪው ህወሀት በኮምቦልቻ ከ100 በላይ የከተማዋን ወጣቶች መጨፍጨፉን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።
አሸባሪው ህወሀት በኮምቦልቻ ከተማ ሰርጎ በመግባት ዛሬ ሌሊቱን ከ100 በላይ የከተማዋን ወጣቶችን አሰልፎ መጨፍጨፉን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።
የሽብር ሀይሉ ሰርጎ በገባበት በደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች የግል እና የመንግስት ሀብቶችን እየዘረፈ እና እያወደመ ነው ሲሉ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶክተር ለገሰ ቱሉ መናገራቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!