የሀገር ውስጥ ዜና

ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ በኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

By Feven Bishaw

November 02, 2021

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 23 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በዓለም ባንክ ከኢትዮጵያ፣ ከኤርትራ፣ ከሱዳንና ከደቡብ ሱዳን ዳይሬክተር ዶክተር ኦስማን ዲዮን እና ባልደረቦቻቸው ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይቱም ወይዘሮ ጫልቱ በኢትዮጵያ የከተሞችን መሰረተ ልማት ለማሻሻልና የከተማን ነዋሪዎች ሕይወት ለመለወጥ በመካሄድ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን በመደገፍ የዓለም ባንክ እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡