የሀገር ውስጥ ዜና

የእስቴ ወረዳ የሚሊሻ አባላት ወደ ግንባር ዘመቱ

By Alemayehu Geremew

November 03, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አሸባሪውን የህወሓት ግፍ “በቃ” ያሉ የደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ ወረዳ የሚሊሻ አባላትና ነዋሪዎች ወደ ጦር ግንባር እየዘመቱ ነው፡፡

ዘማቾቹ ÷አሸባሪው ኃይል ሀገር ለማፍረስ የአማራን እና አፋርን ክልሎች በመውረር የግፍ ግፍ እየፈጸመ በመሆኑ፥ ግፉን ለማስቆም የደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ ወረዳ በሥራ ሃላፊዎች የተመራ የሚሊሻ፣ የፖሊስና ሕዝባዊ ሠራዊት አባላት ወደ ወደ ግንባር መትመም መጀመሩ ነው የተመላከተው፡፡

የአሸባሪው ኃይል ጭካኔ በእያንዳንዱ ደጅ መድረስ የለበትም በማለት ዘማቾቹ በነቂስ መነሳታቸውን የገለጸው የእስቴ ወረዳ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ነው።