አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ጎንደር ዞን እብናት ወረዳ ነዋሪዎች የአማራ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት ያስተላለፈውን የክተት ጥሪ ተቀብለው አሸባሪውን ቡድን ለመፋለም ወደ ጦር ግንባር እየዘመቱ ነው።
አሸባሪውና ወራሪው ቡድን በአማራ ላይ እያደረሰ ያለው ግፍና መከራ ሊበቃ ይገባል፤ከእንግዲህ በኋላ አሸባሪውና ወራሪውን የትግራይ ኃይል የሚሸከም ትክሻ የለንም፤ አርሶ አደሩ ማምረትና ወልዶ ማሳደግ የሚቻለው የአሸባሪውና ወራሪው የትግራይ ኃይል ግብዓተ መሬት ሲፈጸም ብቻ ነው ብለዋል፡፡