Fana: At a Speed of Life!

የጎንደር ከተማን ከሰርጎ ገቦች ለመጠበቅ ጠንካራ አደረጃጀት ተፈጥሯል – ፖሊስ

 

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 25 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የጎንደር ከተማን ከሰርጎ ገቦች ለመጠበቅ ጠንካራ አደረጃጀት ተፈጥሯል ሲል የከተማው ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

የከተማ አሰተዳደሩ አሸባሪውንና ወራሪው የህውሓት ቡድን እና ግብር አበሮቹ በከተማዋ የጥፋት ተልዕኮ እንዳይፈፅሙ በሁሉም የከተማዋ ክፍለ ከተሞች ህዝባዊ አደረጃጀት ተፈጥሮ እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ ሀላፊ ኮማንደር አየልኝ ታክሎ ገልፀዋል።

በግንባር ሂዶ የጠላትን ሀይል መዋጋት እንዳለ ሁኖ ቀሪው የከተማው ማህበረሰብ የጥፋት ሀይሎችን እኩይ ተግባር በመከላከል ረገድ የበኩሉን መወጣት እንዳለበት ሀላፊው ተናግረዋል።

በርካታ የፖሊስ አባላት ወደ ግንባር መዝመታቸውን የተናገሩት ኮማንደር አየልኝ ታክሎ፥ ቀሪዎቹ የፀጥታ አካላት የከተማዋን ሰላም በማስጠበቅ በኩል ሀላፊነታቸውን እየተወጡ መሆኑን አመልክተዋል።

የተፈጠረው ህዝባዊ አደረጃጀት ከአሁኑ ለውጦችን እያመጣ ነው ያሉት ሀላፊው ህዝቡም በንቃት በመሳተፍ ወቅታዊውን የሰላም ስጋት ለመቀልበስ በትጋት እየሰሩ ነው ብለዋል።

አስተያየታቸውን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የሰጡ የከተማዋ ነዋሪዎች፥ አሸባሪው የህውሃት ቡድንና በተግባር የሚመስሉት ተላላኪዎች የጥፋት ሀይሎች ሁከትና አለመረጋጋት በከተማዋ እንዳይፈጥሩ ተገቢውን የአደረጃጀት ክትትል እያደረጉ ናቸው።

ሰርጎ ገቦች ወደ ከተማዋ እንዳይገቡም ከፀጥታ ሀይሉ ጋር በመቀናጀት ተግባሮችን እየመሩ እንደሆነ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

የከተማው ፖሊስ መምሪያም የኢትዮጵያ ጠላቶች ከምድረገፅ እስኩጠፉ ድረስ የከተማው ማህበረሰብ ሁሉን አቀፍ ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል።

በሰላም አስመላሽ

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.