አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 27፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሸባሪዎቹን የህወሓትና የሸኔን ሀገር የማፍረስ ድርጊትን የሚያወግዝ ታላቅ ህዝባዊ ሰልፍ በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል ።
በሰልፉ በዞኑ ከሚገኙ ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።
ሰልፈኞቹ የአሸባሪዎቹን የህወሓትንና የሸኔን ሀገር የማጥፋት የጭካኔ ድርጊቶችን በአንድነት እንመክታለን! ኢትዮጵያ የምትሸነፍ ሀገር አይደለችም !
አከባቢዬን እጠብቃለሁ ሀገሬን ለማዳን እዘምታለዉ!
ሁላችንም በጋራ የጥፋት ሀይሎችን ልንመክታቸዉ ይገባል !
የትህነግን ተልዕኮ የሚያስፈፅሙ በየአካባቢው ተሰግስገው የሚገኙ ባንዳዎችን በማጋለጥ የበኩላችንን ልንወጣ ይገባል ።
በጀግኖቻችን ደምና አጥንት የተገነባች ሀገር በአሸባሪዎቹ የህወሓትና ሸኔ እኩይ ድርጊት አትፈርስም ።
በከሀዲዎች መቃብር ላይ የኢትዮጵያን ብልጽግናን እናረጋግጣለን የሚሉና ሌሎች መፈክሮችን በማሰማት ላይ ይገኛሉ ።
በአበበች ኬሻሞና በኢብራሂም ባዲ
አካባቢዎን ይጠብቁ! ወደ ግንባር ይዝመቱ! መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡ ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!