የሀገር ውስጥ ዜና

የአሸባሪውን ህወሃት ወረራ በመቀልበስ ለኢትዮጵያን ክብር እንቆማለን- የፖለቲካ የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ

By Feven Bishaw

November 07, 2021

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ምንም ዓይነት የፖለቲካ ልዩነት ሳያግደን የአሸባሪውን ህወሃት ወረራ ለመቀልበስ ከመንግስት ጎን ተሰልፈን ለኢትዮጵያ አንድነትና ክብር እንቆማለን ሲሉ በአዲስ አበባ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አረጋገጠ።

በአዲስ አበባ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሙሉጌታ አበበ ለሰልፈኛው ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት፥ ኢትዮጵያ ከማንምና ከማንም በላይ ናት፤ የፖለቲካ ልዩነትም ከሀገር በታች ነው ብለዋል።