የሀገር ውስጥ ዜና

ሩሲያ የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና አንድነት እንዲከበር ያላትን ቁርጠኝነት በድጋሜ አረጋገጠች

By Feven Bishaw

November 09, 2021

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 30 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በተባበሩት መንግስታት የሩሲያ ምክትል ቋሚ ተጠሪ አና ኢቭስቲኒቫ የፀጥታው ምክር ቤት የአፍሪካን ሰላም እና ደህንነትን አስመልክቶ ትናንት ባካሄደው ስብሰባ ላይ ሀገራቸው የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ለማስጠበው ያላትን ቁርጠኛ አቋም ዳግም አደጋገጡ።

በአፍሪካ ቀንድ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ ተወካይ ኦሊሴጎን ኦባሳንጆ እና የፖለቲካ እና የሰላም ግንባታ ጉዳዮች ምክትል ዋና ፀሃፊ ሮዝሜሪ ዲካርሎ በሰሜን ኢትዮጵያ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ የሰጡትን ማብራሪያ እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ ተሳትፎም ተቀባይነት ያለዉ ነዉ ብለዋል፡፡