በኢትዮጵያ የአርሜኒያ አምባሳደር አርቴም አዝናውሪያን ለስራ ጉብኝት ድሬዳዋ ገቡ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አምባሳደሩን የድሬዳዋ ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን እና የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊው አቶ ሚካኤል እንዳለ ድሬዳዋ አለም አቀፍ ኤርፖርት በመገኘት አቀባበል አድርገውላቸዋል።
አርመናውያን ከድሬዳዋ ጋር ጥንታዊ የታሪክና የባህል ትስስር እንዳላቸው የገለፁት የባህልና ቱሪዝም ጽ/ቤት ኃላፊው÷ አምባሳደሩ በድሬዳዋ ቆይታቸው የተለያዩ ታሪካዊ ቦታዎችን እንደሚጎበኙ እና ከከፍተኛ አመራሮች ጋር እንደሚወያዩ አስታውቀዋል።
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!