ቢዝነስ

ከኤሌክትሮኒክስና ኮሙኒኬሽን ዕቃዎች 3 ነጥብ 7 ሚሊየን ዶላር ተገኘ

By Alemayehu Geremew

November 10, 2021

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 1 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ወደ ውጪ ከተላከ የኤሌክትሪክ ኤሌክትሮኒክስና ኮሙኒኬሽን ዕቃዎች 3 ነጥብ 7 ሚሊየን ዶላር ገቢ ተገኝቷል፡፡

የኤሌክትሪክ ኤሌክትሮኒክስና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ፀሀዬ ይነሱ፥ የማምረቻ ኢንዱስትሪውን የግብይት አቅም ለማሳደግ የምርትና የግብዓት ትስስር የመፍጠርና ቅንጅታዊ አሰራርን የማጎልበት ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።

ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ በተሰሩ ስራዎች 4 ፕሮጀክቶች ወደ ማምረት የተሸጋገሩ ሲሆን ሶስት ኢንተር ፕራይዞች ደግሞ የማስፋፊያ ስራ መከናወኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።