የሀገር ውስጥ ዜና

በድሬዳዋ ማንኛውም አካል የጦር መሳሪያውን እንዲያስመዘግብ ጥሪ ቀረበ

By ዮሐንስ ደርበው

November 11, 2021

 

አዲስ አበባ፣ ህዳር 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የድሬዳዋ ፖሊስ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልከቶ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

ማንኛውም በድሬዳዋ ከተማ እና ገጠር ውስጥ የሚገኝ ግለሰብ ፣ መንግስታዊም ሆነ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅትና መስሪያ ቤት በእጁ የሚገኘውን የጦር መሳሪያ ፍቃድ ቢኖረውም ባይኖረውም በአቅራቢያው በሚገኝ የቀጠናው ፖሊስ ጣቢያ ድረስ በግንባር በመሄድ ማስመዝገብ እንዳለበት አሳስቧል፡፡

ፖሊስ እንዳስታወቀው ከህዳር 2 እስከ ህዳር 3 ቀን 2014 ዓ.ም ባሉት ሁለት ቀናት ውስጥ ማንኛውም ግለሰብ፣ መንግስታዊም ሆነ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅትና መስሪያ ቤት በእጁ የሚገኘውን የጦር መሳሪያ ሳያስመዘግብ ቢቀር ተገቢውን እርምጃ ይወሰድበታል ማለቱን የድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽን መረጃ ያመላክታል::

አካባቢዎን ይጠብቁ!

ወደ ግንባር ይዝመቱ!

መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡- ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!