የሀገር ውስጥ ዜና

በዶ/ር ኢ/ር ስለሺ የተመራ ልኡክ ከግብፅና ሱዳን ጋር የተደረገውን የህግ ማዕቀፍ ድርድር ውጤት በዋሽንግተን ዲሲ መገምገም ጀመረ

By Tibebu Kebede

February 11, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በውሃ፣ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ የተመራው የኢትዮጵያ ልኡክ በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ከግብፅ እና ሱዳን ልዑካን ጋር የተደረገውን የህግ ማዕቀፍ ድርድር ውጤት በዋሽንግተን ዲሲ መገምገም ጀመረ።

ሚኒስትሩ የህግ ማዕቀፍ ድርድር ውጤቱን ለመመልከት በትናንትናው እለት አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ መግባታቸውን በትዊተር ገፃቸው አስታውቀዋል።