የሀገር ውስጥ ዜና

ኢትዮጵያና ብሪታኒያ በትብብር መስራት የሚችሉባቸውን ጉዳዮች በመለየት ድጋፍ እናደርጋን-የብሪታኒያ አምባሳደር

By Feven Bishaw

November 12, 2021

 

አዲስ አበባ፣ ህዳር 3 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዶክተር በለጠ ሞላ በኢትዮጵያ ከብሪታኒያ አምባሳደር ዶክተር አላሰቴይር ማክፌይልን ጋር ተወያዩ፡፡

በውይይቱ ዶክተር  በለጠ ኢትዮጵያና ብሪታኒያ የረጅም ዘመናት የቆየ ታሪካዊ ግንኙነት ያላቸው መሆኑን አውስተው ይህን ግንኙነት የጋራ ተጠቃሚነትን በሚያረጋግጡ መስክች ማጠናከርና ማስቀጠል እንደሚገባ ገልጸውላቸዋል።