የሀገር ውስጥ ዜና

ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ከተመድ የፖለቲካና የሰላም ግንባታ ጉዳዮች ዋና ፀሃፊ ጋር ተወያዩ

By Tibebu Kebede

February 11, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፖለቲካ እና የሰላም ግንባታ ጉዳዮች ዋና ፀሃፊ ጋር ተወያዩ።

ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል በተመድ የፖለቲካ እና የሰላም ግንባታ ጉዳዮች ዋና ጸሀፊ ሮዝሜሪ ዲያካርሎ፣ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ዋና ፀሀፊን ፓርፌት ኦናጋ አናያንጋን እና የተመድ የነዋሪዎችና እና የሰብዓዊ ጉዳዮች የኢትዮጵያ አስተባባሪ ዶክተር ካትሪን ሶዚን ዛሬ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል።