የሀገር ውስጥ ዜና

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል አውሮፕላኖችን በኬሚካል የማፅዳት ስራ እያከናወነ ነው

By Tibebu Kebede

February 11, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል አውሮፕላኖችን በኬሚካል የማፅዳት ስራ በማከናወን ላይ ይገኛል።

አየር መንገዱ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ከሚያደርጋቸው ከፍተኛ ቅድመ ጥንቃቄዎች አንዱ ከቻይና እና ቫይረሱ ከታየባቸው ሀገራት የሚመጡ አውሮፕላኖችን በኬሚካል የማፅዳት ስራ መሆኑንም አስታውቋል።