የሀገር ውስጥ ዜና

ዳያስፖራው የሀገሩን ሰላም ለማስጠበቅ የሚያደርገውን ተሳትፎ እንዲያጠናክር ተጠየቀ

By Tibebu Kebede

February 11, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 3፣ 2012 (ኤፍ ቢ ) የዳያስፖራው ማህበረሰብ የሀገሩን ሰላም ለማስጠበቅ የሚያደርገውን ሁለንተናዊ ተሳትፎ አጠናክሮ እንዲቀጥል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ጥሪ አቀረቡ።

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማህበር ”ዳያስፖራው ለሀገር ሰላም ግንባታ” በሚል መሪ ሃሳብ በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ጋር በአዲስ አበባ ውይይት አካሂዷል።