አዲስ አበባ፣ ህዳር 13፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) “የአየር ብክለትን በመቀነስ፣ መሰረታዊ የጤና እና የስርዓተ ምግብ አገልግሎቶች ጥራትን በማሻሻል በሳምባ ምች የሚሞቱ ህፃናትን እናትርፍ” በሚል መሪ ቃል የዓለም የሳንባ ምች ቀን በጅግጅጋ ከተማ ተከብሯል።
የሶማሌ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ መሃሙድ መሃመድ አብዲ÷ ከሳንባ ምች በሽታ ጋር ተያይዞ ይደርሱ የነበሩ ችግሮች ላይ መሻሻሎች መኖራቸውን ተናግረዋል።