አዲስ አበባ፣ ህዳር 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ “ኢትዮጵያ” የሚለውን የነጻነት ስም የማስጠበቅ የታሪክ አደራ አለብን በሚል ያስተላለፉትን መልዕክት ተከትሎ ነው ከፍተኛ አመራሩ ዝግጁነቱን ያስታወቀው፡፡
የብልጽግና ፓርቲ ትናንት ባካሄደው ስብሰባ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በጦር ግንባር በመገኘት ጦሩን ለመምራት እንደሚሄዱ አስታውቀው በዛሬው ዕለትም ወደ ግንባር ተጉዘዋል፡፡