የሀገር ውስጥ ዜና

ሀገር የማፍረስ ዓላማን ያነገቡ አሸባሪዎች እያደረጉት ያለውን እንቅስቃሴ ለመቀልበስ መስራት ይገባል- አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን

By Feven Bishaw

November 25, 2021

 

አዲስ አበባ፣ ህዳር 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀገር የማፍረስ ዓላማን ያነገቡ አሸባሪዎች ከአገር ውስጥ እና ከውጭ አጋሮቻቸው ጋር በመሆን እያደረጉት ያለውን እንቅስቃሴ ለመቀልበስ በጠንካራ ትብብር መስራት እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ተናገሩ።

ሚኒስትር ዴኤታው ይህን ያሉት ዛሬ “ዲፕሎማሲያችንን በአዲስ ምዕራፍ ለላቀ ለውጥ” በሚል መሪ ቃል የሚሲዮን መሪዎችና የዋናው መስሪያ ቤት የስራ ኃላፊዎች ዓመታዊ ስብሰባ ሲጀመር ነው።