አዲስ አበባ፣ ህዳር 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀገር የማፍረስ ዓላማን ያነገቡ አሸባሪዎች ከአገር ውስጥ እና ከውጭ አጋሮቻቸው ጋር በመሆን እያደረጉት ያለውን እንቅስቃሴ ለመቀልበስ በጠንካራ ትብብር መስራት እንደሚገባ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ተናገሩ።
ሚኒስትር ዴኤታው ይህን ያሉት ዛሬ “ዲፕሎማሲያችንን በአዲስ ምዕራፍ ለላቀ ለውጥ” በሚል መሪ ቃል የሚሲዮን መሪዎችና የዋናው መስሪያ ቤት የስራ ኃላፊዎች ዓመታዊ ስብሰባ ሲጀመር ነው።