የሀገር ውስጥ ዜና

የሀረሪ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች ለመከላከያ ሰራዊት ደም ለገሱ

By Feven Bishaw

November 25, 2021

 

አዲስ አበባ፣ህዳር 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀረሪ ክልል የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች የአሸባሪውን የህወሃት ኃይል ለመደምሰስ በህልውና ዘመቻ ላይ መስዋዕትነት እየከፈለ ለሚገኘው ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ደም ለግሰዋል፡፡

ለሀገር መቆም ማለት ግንባር ድረስ በመሄድ ከጠላት ጋር መፋለም ብቻ ሣይሆን ለሀገሪቱ እድገት ሁሉም በያለበት ተቋም እና ስራ ህብረተሰቡን በንቃትና በታማኝነት በማገልገል ማስመስከር እንደሚገባም ነው ሠራተኞች የገለጹት፡፡