የሀገር ውስጥ ዜና

በመዲናዋ 100 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የሞተር አልባ ትራንስፖርት መስመር ሊዘረጋ ነው

By Tibebu Kebede

February 12, 2020

አዲስ አበባ፣ የካቲት 4፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ በሚቀጥሉት 10 አመታት መቶ ኪሎሜትር የሚሸፍን የሞተር አልባ ትራንስፖርት መስመር ሊዘረጋ ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ የትራፊክ ማኔጅመንት ቢሮ በከተማዋ በአዲስ መልክ ሊተገበር የታሰበውን የሞተር አልባ ትራንስፖርት አገልግሎትን በተመለከተ ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎችና ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አድርጓል፡፡