አዲስ አበባ፣ህዳር 17፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል ጌዴኦ ዞን ዲላ ከተማ በወጣት አደረጃጀት አስተባባሪነት “እኔም የዘማች ቤተሰብ አካል ነኝ̍” በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት በወጣቶች እና በክልል ከፍተኛ አመራሮች በይፋ ተጀመረ::
ኢትዮጵያውያን ጀግኖችን የወለዱ፣ ለአገራቸው የሚዋጉ እና ጠላትን የሚያንበረክኩ ጀግና እናቶች አሉን ሲሉ የደቡብ ክልል ወሳኝ ኩነቶች ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ አጋፋሪ ተናግረዋል፡፡