አዲስ አበባ፣ ህዳር 19፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ)ኢትዮጵያ ስትፈራርስ ከማየት በላይ ውርደት ባለመኖሩ መሞት ካለብን አሸባሪው ሕወሓትን ለማስቆም በሚደረግ ትግል ላይ መሰዋት የተሻለው አማራጭ መሆኑን የኢዜማ መሪና የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገለጹ።
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ ስትፈራርስ ከማየት በላይ ውርደት የለም። ያንን ውርደት ላለማየት አሸባሪው ሕወሓትን ለማስቆም በሚደረግ ትግል ላይ መሰዋት የተሻለው አማራጭ ነው ብለዋል።