Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ተንታ፣ ማሻና ወግዲ ከተሞች የኤሌክትሪክ ሃይል አገኙ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ተንታ፣ ማሻና ወግዲ ከተሞች ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ አገልግሎት በድጋሚ ማግኘታቸውን የአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል፡፡

የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት የወደመባቸውን ከተሞች የኤሌክትሪክ አስተላላፊ መስመሮችንና ምሰሶዎችን በመጠገን ነፃ የወጡ ከተሞችን ከስር ከስር እተከተለ የኤሌክትሪክ ኃይል መልሶ የማገናኘት ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል፡፡

በዚህም ተንታ፣ ማሻና ወግዲ ከተሞች የሚያገኙበትን የመካከለኛና የዝቅተኛ መስመር ጥገና በማጠናቀቅ አገልግሎቱን ትላንትና ዛሬ ጠዋት እንዲያገኙ መደረጉን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version