Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በቀራኒዮ ፀበል አካባቢ በደረሰ ቃጠሎ የአንድ ቤተሰብ አባል የሆኑ 5 ሰዎች ህይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ልዩ ዞን በተለምዶ ቀራኒዮ ፀበል እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በደረሰ የመኖሪያ ቤት ቃጠሎ የአምስት ሰዎች ህይወት አለፈ።
ትናንት ከምሽቱ 5:34 አካባቢ በደረሰው የመኖሪያ ቤት ቃጠሎ አምስት የአንድ ቤተሰብ አባላት ህይወት ማለፉን የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
በአደጋው አባትን ጨምሮ ከ4 እስከ 14 ዓመት እድሜ የነበራቸው ህጻናት ናቸው ህይወታቸው ያለፈው።
አደጋውን ለመከላከል 25 የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች 3 ከባድ ተሽከርካሪ 2 አምቡላንስ 2 ቀላል ተሽከርካሪ የተሰማሩ ሲሆን÷ በአደጋው 200 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል፡፡
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version