Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በሱዳን የብሉናይል ግዛት ከፍተኛ አመራሮች ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ገቡ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሱዳን ሪፐብሊክ የብሉናይል ግዛት ከፍተኛ አመራሮች ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ገብተዋል።
 
የግዛቱ ከፍተኛ አመራሮች ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሲገቡ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰንን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸዋል።
 
የሁለቱ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በድንበር አካባቢ ባለው የጸጥታ፣ የጋራ የድንበር ልማት ትብብር ዙሪያ በጋራ መስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ይወያያሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
Exit mobile version