Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የቁልቢ ገብርኤል በዓለ ንግስ በሰላም ተጠናቋል -የድሬዳዋ ፖሊስ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 19 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቁልቢ ገብርኤል በዓለ ንግስ በሰላም ተከብሮ መጠናቀቁን የድሬ ዳዋ ፖሊስ ገለፀ።
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት የሚከበረው የቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል በአለ ንግስ በዛሬው እለት በርካታ የበአሉ አክባሪዎች በተገኙበት ያለምንም የፀጥታ ችግርና የትራፊክ አደጋ ሳይከሰት በሀይማኖታዊ ስርአቱ መሰረት በሰላም ተከብሯል።
ለበዓለ ንግሱ በሰላም መከበር ህዝበ ምዕመኑ፣ መላው የአስተዳደሩ ነዋሪና የፀጥታ ሀይሉ ለነበረው አስዋጽኦና እገዛ ብሎም ውጤታማ ድርሻ ፖሊስ ምስጋናውን አቅርቧል::
አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version