Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በህወሃት የሽብር ቡድን የወደሙ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት በመረባረብ ሊፈጠር የሚችልን ስራ አጥነት ማስቀረት ይግባል – አቶ ንጉሱ ጥላሁን

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሥራ እና ክህሎት ሚኒስቴር በተሻሻለው የኢንተርፕራይዞች ልማት ስትራቴጂ ላይ ሥልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

ሥራ አጥነት ኢኮኖሚያዊ ፣ ማኅበራዊ እና በዜጎች ላይ ሥነ-ልቦናዊ ጫና የሚያስከትል በመሆኑ ችግሩን ለማቃለል የመርሃ ግብሩ ሰልጣኞች ስትራቴጂ፣ ደንብ ፣ መመሪያ እና ሌሎችንም የድጋፍ ማዕቀፎች መሠረት አድርገው በመስራት የሚሊየኖችን ጥያቄ መመለስ እንዲቻል ትልቅ ኃላፊነት ወስደው ሊሰሩ እንደሚገባ የሥራ እና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ንጉሱ ጥላሁን ገልጸዋል፡፡

በአማራ እና በአፋር ክልሎች በኢንተርፕራይዞች ላይ ከፍተኛ ውድመት መድረሱን አቶ ንጉሱ ጠቁመዋል።

እነዚህን አካባቢዎች በርብርብ መልሶ መገንባት ወይም መጠገን ካልተቻለ በክልሎቹ ሥራ አጥነት እንደሚጨምርና የኢኮኖሚው ትልቅ ህመም ሆኖ እንደሚቀጥል መግለፃቸውን ከሥራ ክህሎት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version