Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ከቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች መምሪያ ዋና ዳይሬክተር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 21፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቻይና የኢትዮጵያ አምባሳደር ተሾመ ቶጋ ከሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች መምሪያ ዋና ዳይሬክተር ው ፔንግ ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡

ውይይቱ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ ማለትም ከግጭት በኋላ ስለሚደረገው መልሶ ግንባታ እና ከኮቪድ-19 ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው ተብሏል፡፡

ሁለቱም ወገኖች ሀገራቱ በቀጣይ ሊሰሩባቸው የሚችሉ የትብብር ዘርፎችን መለዋወጣቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የማህበራዊ ትስስር ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version