Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የቄለም ወለጋ ዞን አባገዳዎች እና ሀደ ሲንቄዎች ለሸፈቱ ታጣቂዎች የሠላም ጥሪ አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቄለም ወለጋ ዞን የሚገኙ አባገዳዎች እና ሀደ ሲንቄዎች ለሸፈቱ እና ጫካ ለገቡ ታጣቂዎች ለመንግስት እጅ እንዲሰጡ እና በሠላም ወደ ኅብረተሰባቸው እንዲቀላቀሉ ጥሪ አቀረቡ፡፡

የዞኑ አባገዳዎች እና ሀደ ሲንቄዎች “ለሀገራችን የሰላም ጊዜ ነው ፤ መሳሪያ ታጥቆ ጫካ መግባት፣ ደም ማፍሰስና ንብረት ማውደም አያስፈልግም” ብለዋል በጥሪያቸው።

“ማንኛውም ለኅብረተሰቡ እታገላለሁ የሚል አካልም ሀሳቡን በነጻነት በሰላማዊ መንገድ መግለጽ አለበት እንጂ ጫካ መግባት አያስፈልግም” ሲሉም በጥሪያቸው መምከራቸውን ከቄለም ወለጋ ዞን ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version