Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በመተማ ወረዳ የ6 ዓመት ህፃን ያገቱ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 2፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳ ዲቢኮ ቀበሌ የ6 ዓመት ህፃን ያገቱ 4 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የወረዳው ሰላምና ደህንነት ጽህፈት ቤት አስታወቀ፡፡
የመተማ ወረዳ አስተዳደር የፀረ ሽምቅ ጋንታ አመራር ፶ አለቃ ባየ ደጉ እንደገለጹት፥ ከዲቢኮ የጸጥታ አካላት እንዲሁም ከማህበረሰቡ ጋር በቅንጅት በተካሄደ ኦፕሬሽን የማገት ወንጀሉን የፈፀሙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
ድርጊቱን ያወገዙት ፶ አለቃ ባየ፥ ማህበረሰቡ በንቃት አካባቢውን እና ቤተሰቡን እንዲጠብቅ አሳስበው፥ ችግሮች ሲኖሩም ከጸጥታ አካላት ጋር በጋራ የጸጥታ ስራ መስራት እንዳለበት ማሳሰባቸውን ከመተማ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
በአካባቢው ገንዘብ ለመቀበዕል ሲሉ አንዳንድ ሰዎች በዚህ የወንጀል ድርጊት እየገቡና ህብረተሰቡን እያስመረሩ መሆኑ በተለያየ ጊዜ ሲነሳ ይስተዋላል፡፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version