Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በምስራቅና ደቡብ አፍሪካ የዓለም ባንክ ዳይሬክተር ዑስማን ዲዮን የተመራ ልኡክ ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ገባ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 11፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምስራቅና ደቡብ አፍሪካ የዓለም ባንክ ዳይሬክተር ዑስማን ዲዮን የተመራ ልኡክ ሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ገብቷል።
ልኡኩን የሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ ፣የሶማሌ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኢብራሂም ኡስማንና ከፍተኛ የክልሉ የስራ ሀላፊዎች በጅግጅጋ ገራድ ዊልዋል ኤርፖርት በመገኘት አቀባበል አድርገውላቸዋል።
የልዑካን ቡድኑ በቆይታው በክልሉ በተከሰተው ድርቅ ዙሪያም ከክልሉ ፕሬዚዳንትና ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች ጋር ይመክራል ተብሎም እንደሚጠበቅ ከክልሉ ብዙሃን መገናኛ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version