Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ዕረፍት የተሰማቸውን ሀዘን ገለፁ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 25፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አራተኛው ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ በማረፋቸው ሀዘን እንደተሰማቸው ገለፁ።
ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባወጡት መግለጫ በቅዱስነታቸው ዜና ዕረፍት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን በራሳቸውና በከተማ አስተዳደሩ ስም ገልፀዋል።
የቅዱስነታቸውን ነብስ ፈጣሪ በአፀደ ገነት ያኖረው ዘንድ እንደሚመኙም ገልፀዋል።
Exit mobile version