አዲስ አበባ፣የካቲት 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ትልቁ የማህበራዊ የስራ ፈጠራ ውድድር በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሊካሄድ መሆኑን ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ፡፡
የፈጠራ ውድድሩን ሀልት ፕራይዝ ፋውንዴሽን ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የሚያካሄድ ሲሆን በወድድሩ ለመሳተፍ የፈጠራ ክህሎት ያላቸው ተማሪዎች እየተመዘገቡ መሆናቸው ተመላክቷል፡፡
ሀልት ፕራይዝ ለትርፍ ያልተቋቋመ ድርጅት ሲሆን በአሜሪካ ውስጥ በተካሄደው የፍጻሜ ውድድር ላይ የሚሰጠውን የ1 ሚሊየን ዶላር ሽልማት ሀሳብ ለማውጣት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ሀሳብ ያወዳድራል።
ወድድሩ መጋቢት 16 ቀን አሉሙኒየም የመሰብሰቢያ አዳራሽ እንደሚካሄድ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡ ፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!