Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የአፋር ክልል ምክር ቤት ስድስተኛ የስራ ዘመን አንደኛ መደበኛ ጉባኤ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክር ቤት ስድስተኛ የስራ ዘመን አንደኛ ዓመት አንደኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ በሠመራ ከተማ ተጀመረ።
ጉባኤው እስከ መጋቢት 14 ቀን 2014 ዓ.ም በሚያደርገው ቆይታ በተለያዩ ወቅታዊ አጀንዳዎች ዙሪያ እንደሚመክር ይጠበቃል።
የአስፈጻሚ አካላት የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ በመወያየት ቀጣይ አቅጣጫዎችንም ማስቀመጥ ከምክር ቤቱ ጉባኤ አጃንዳዎች መካከል እንደሚገኙበት ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version