Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

104 ኢትዮጵያውያን ከታንዛኒያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 18፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ሰለባ የሆኑ 104 ኢትዮጵውያን በዛሬው ዕለት ከታንዛኒያ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል።

ተመላሾቹ ኢሪንጋ በሚባለው ግዛት በሚገኝ እስር ቤት ውስጥ የቆዩ መሆናቸውን በታንዛኒያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታውቋል።

በቅርቡ ሞሮጎሮ፣ ሩቩማ፣ ንጆም፣ ቤምቤያ እና ሶንግዌ በሚባሉ የታንዛኒያ ግዛቶች ታስረው የነበሩ 294 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው መመለሳቸው ይታወሳል።

Exit mobile version