Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በአቶ አሕመድ ሺዴ የተመራ ልዑክ በዓለም ባንክ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ዋሺንግተን ዲሲ ገባ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 10 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሺዴ የተመራ ልዑክ በዓለም ባንክ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም አመታዊ ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ዋሺንግተን ዲሲ ገባ።
ልዑኩ በቆይታው ከስብሰባው ባለፈ የሁለትዮሽና የባለ ብዙ ወገን ምክክር እንደሚያደርግ በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍጹም አረጋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዢ ዶክተር ይናገር ደሴ እና የገንዘብ ሚኒስትር ዲኤታ ዶክተር እዮብ ተካልኝ ከገንዘብ ሚኒስትሩ ጋር ወደስፍራው አቅንተዋል።
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version