Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ማንቼስተር ዩናይትድ ኤሪክ ቴን ሃግን በሦስት ዓመት ውል ማስፈረሙን አስታወቀ

አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 13 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የእንግሊዙ እግር ኳስ ክለብ ማንቼስተር ዩናይትድ ኤሪክ ቴን ሃግን በሶስት አመት ውል ማስፈረሙን አስታወቀ።

የ52 አመቱን አሰልጣኝ ሊራዘም በሚችል የአንድ አመት ተጨማሪ ኮንትራት ለሶስት አመታት ከሆላንዱ አያክስ አምስተርዳም ማስፈረሙን ክለቡ ይፋ አድርጓል።

የእንግሊዙ ክለብ አሰልጣኙን ማስፈረሙን ተከትሎ ለአያክስ የኮንትራታቸውን ማካካሻ የሚከፍል ይሆናል።

አዲሱ አሰልጣኝ በውጤት ቀውስ የሚገኘውን ክለብ መልሶ የመገንባት ቀዳሚ ስራ ይጠብቃቸዋል ተብሏል።

የላንክሻየሩ ክለብ ከአሰልጣኝ አሌክስ ፈርጉሰን መልቀቅ በኋላ የሊግ ዋንጫ አሸንፎ አያውቅም።

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version