Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ዶክተር ፍጹም አሰፋ ከጃፓን ልማት የትብብር ኤጀንሲ ልኡክ ጋር ተወያዩ

 

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የፕላን እና ልማት ሚኒስትር ዶክተር ፍጹም አሰፋ ከጃፓን ልማት የትብብር ኤጀንሲ (ጃይካ) ልኡክ ጋር ተወያይተዋል፡፡

ዶክተር ፍጹም በፕሮፌሰር ኬኒቺ ኦህኖ ከተመራው የኤጀንሲው ልኡክ ጋር የአስር ዓመት የልማት ዕቅድ አተገባበር እንዲሁም ያለበት ደረጃ፣ ውጤት እና ያጋጠሙ ችግሮች ላይ መክረዋል፡፡

በተጨማሪም የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አተገባበር እና የታለመላቸውን ውጤት ያመጣ ስለመሆኑ ነባራዊ ሁኔታውን ያገናዘበ የሦስት ዓመት ዕቅድ ተግባራዊነት ውጤታማነት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

Exit mobile version